ፀሀይ ማታ ዘልቃ
እዚህ ጎኔ ወድቃ
ለኔ ብቻ ደምቃ
እኔን ብቻ አሙቃ
እንዲህ ትለኛለች
“እኔና ሙቀቴ
ክንድሽ መቀነቴ
ደረትሽ ሌማቴ
ጣይን ያክል ግለት ይዤ በገላዬ
ቀለጥኩ ጡቶችሽ ስር ካለም ተነጥዬ”
እኔም እላታለሁ
ውብ አይኗን እያየሁ
“እንዲህ እንደሆንን እንደጋምኩ ካንቺጋ
የሰማይ ክዳኑ ይጠርቀም ይዘጋ
እንደተወሳሰብን ዘላለም አይንጋ “
#የአመጻግጥሞች #theforbiddenlyrics
ግጥም እፅፋለሁ ላንቺ ላንቺ ብቻ
ቃላት ተናጥቄ ቤት መድፊያ ቤት መምቻ
ያለም ቅኔና ቃል ይበቃሻል ወይ
ስጽፍ ስፅፍ ውዬ ሲያነቡሽ እንዳይ
#የአመጻግጥሞች #Theforbiddenlyrics
ሊሊት የቃቄዋ
Like this:
Like Loading...
Related
Published by Queer Ethiopia
"Queer family" is an alternative space created by a group of queer Ethiopian women. It is designed to be a space for a diverse group of Ethiopian queer women whose sexual and gender identifications vary. It includes cis and trans women who may be lesbian, bisexual or asexual. This is a space where the experiences of queer people takes center stage. We hope to include personal experiences from our daily lives as queer people, various stories, interviews, original artwork and poetry. We hope it will also serve as a place where Ethiopians in Ethiopia and Ethiopians in the diaspora come as themselves to explore and create an online community.
If you would like to send us something, please send us an email via etqueerfamily@gmail.com
«ኩዊር ኢትዮጵያ» የተለያዩ ፆታዊና ወሲባዊ ዝንባሌ ላላቸው ኢትዮጵያዊ ኩዊር ሴቶች እንዲሆን ታስቦ በኩዊር ሴቶች የተመሠረተ አማራጭ ምኅዳር ነው። ይኽውም ሌዝቢያን፣ ባይሴክሽዋል ወይም ኤሴክሽዋል የሆኑ ሴቶችንንና ትራንስ ሴቶችን ያካትታል። ይህ ምኅዳር የኩዊር ማኅበረሰብ ታሪክ እና የሕይወት ልምድ ትልቅ ሥፍራ የሚይዝበት ነው። እንደ’ኩዊር ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወታችንን ገጠመኞች፤ የተለያዩ ሰዎችን የግል ታሪኮች፤ ቃለ-
መጠይቆች እንዲሁም ሥነ-ጥበባትን እንደምናካትት ተስፋ እናደርጋለን። ከነዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዳያስፖራ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ራሳቸውን ሆነው
የሚመጡበት የበይነ-መረብ ማኅበረሰብ መድረክ ሆኖ እንዲያገለግል ማስቻል ፍላጎታችን ብቻ ሣይሆን ጥረታችንም ጭምር ነው።
etqueerfamily@gmail.com
View all posts by Queer Ethiopia