የኢትዮ ኩዊር የቅርብ ጊዜ ፖድካስት በሶስት ቀናት ውስጥ ሊወጣ የታቀደ ሲሆን ከአዲስ አበባ ውጪ የሚኖሩ የLBTQ ማህበረሰብ የሚገጥማቸውን ፈተና አስመልክቶ አስደናቂ እና ጠቃሚ ውይይት ነበረን።
አዲስ አበባ ለLBTQ ማህበረሰብ ምቹ ቦታ አለው ብሎ ማሰብ ይከብዳል ነገር ግን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በክልል ከተማ ትኖር ከነበረችው ዮሃን ጋር ያደረግነው ውይይት ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ ክልል ከተሞች ላይ LBTQ መሆን ይበልጥ ከባድ እንደሆነ የመገንዘብን አስፈላጊነት አጉልቶ ያሳያል። ከዚህ በታች ከዮሃን ጋር ካደረግነው ውይይት የተቀነጨቦ ሃሳቦችን አካተናል። በሶስት ቀናት ውስጥ የሚለቀቀው ፖድካስት https://soundcloud.com/ethioqueer ላይ ሊደመጥ ይችላል።
“እራሴን አስራ አንደኛ ክፍል ላይ እራሴን ተቀበልኩኝ። ክፍለ ሃገር ላይ ብዙም ሰው የለም እና ብቸኝነት በጣም ነበር የሚሰማኝ። ቤተክርስቲያን ስሄድ በራሱ ሁሉም ሰው የሚያውቅብኝ ነበር የሚመስለኝ ገና ሲያዩኝ ስለኔ እያሰቡ ይሆን እንዴ ብዬ እጨናነቅ ነበር።”
“አዲስ አበባ እና ክልል ከተሞች ላይ ትልቅ ልዩነት አለው። ክልል ከተሞች ላይ ሰው ኣታገኚም በተለይ እኔ የነበርኩበት ቦታ ሰው አለ ይባላል ግን እኔ እንደሚመስለኝ ሰው ካለ ሁሉ እዛ መኖር አይፈልግም ምክንያቱም ብዙ ኮኔክሽን የለም፣ ብዙም ልትገናኚም ስለማትችዪ ሰው ማንነቱን ፍልጋ እና ለመኖር ብሎ ክክልል ከተሞች ይውጣል። ብዙ ይኛ ኮሚዩኒቲ የሚገኘው በአዲስ አበባ ነው። አብዛኛው ሰው ወደ አዲስ አበባ የሚምጣ ይመስለኛል። አዲስ አበባ የመጣሁበት አንደኛ ምክንያቴ በማንነቴ ነው፣ ሌዝቢያን በመሆኔ ነው።”
“ባልረፈደ ግዜ ነው ራሴን የተቀበልኩት ግን እዚህ [አዲስ አበባ]ቢሆን ግን ያንን ሁሉ ስቃይ አላሳልፍም ነበር። እዛ [የክልል ከተማ]እያለሁ ብቸኝነት በጣም ይሰማኝ ነበር እዚህ ቢሆን ግን የዛን ያህል አይሰማኝም ነበር ብዬ አሰባልሁ። ለጎደኛዬም መጨረሻ ላይ ያነገርኳት የመታፈን ስሜት ስለተሰማኝ ነው።“
Like this:
Like Loading...
Related
Published by Queer Ethiopia
"Queer family" is an alternative space created by a group of queer Ethiopian women. It is designed to be a space for a diverse group of Ethiopian queer women whose sexual and gender identifications vary. It includes cis and trans women who may be lesbian, bisexual or asexual. This is a space where the experiences of queer people takes center stage. We hope to include personal experiences from our daily lives as queer people, various stories, interviews, original artwork and poetry. We hope it will also serve as a place where Ethiopians in Ethiopia and Ethiopians in the diaspora come as themselves to explore and create an online community.
If you would like to send us something, please send us an email via etqueerfamily@gmail.com
«ኩዊር ኢትዮጵያ» የተለያዩ ፆታዊና ወሲባዊ ዝንባሌ ላላቸው ኢትዮጵያዊ ኩዊር ሴቶች እንዲሆን ታስቦ በኩዊር ሴቶች የተመሠረተ አማራጭ ምኅዳር ነው። ይኽውም ሌዝቢያን፣ ባይሴክሽዋል ወይም ኤሴክሽዋል የሆኑ ሴቶችንንና ትራንስ ሴቶችን ያካትታል። ይህ ምኅዳር የኩዊር ማኅበረሰብ ታሪክ እና የሕይወት ልምድ ትልቅ ሥፍራ የሚይዝበት ነው። እንደ’ኩዊር ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወታችንን ገጠመኞች፤ የተለያዩ ሰዎችን የግል ታሪኮች፤ ቃለ-
መጠይቆች እንዲሁም ሥነ-ጥበባትን እንደምናካትት ተስፋ እናደርጋለን። ከነዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዳያስፖራ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ራሳቸውን ሆነው
የሚመጡበት የበይነ-መረብ ማኅበረሰብ መድረክ ሆኖ እንዲያገለግል ማስቻል ፍላጎታችን ብቻ ሣይሆን ጥረታችንም ጭምር ነው።
etqueerfamily@gmail.com
View all posts by Queer Ethiopia