ፖድካስት፡ የ”ወንዳወንድ” ሴት ህይወት በኢትዮጵያ

የዚህ ወር ፖድካስታችን በአንድ የክልል ከተማ የምትኖረውን ዮርዳኖስን ይዛላችሁ መጥታለች። ዮርዳኖስ በተለምዶ “ወንዳወንድ” የምትባል ሌዝቢያን ናት፥ ስርዐተ ፆታን ለእርሷ ትርጉም በሚሰጥ መልኩ እንደገና በመተርጎም ፥ የስርዐተ ፆታ ማንነቶችንን ወይም የስርዐተ ፆታ አገላለጾችን ዋጋ በማይሰጥ  ሀገር ውስጥ መኖር፥ በሰፊው ማህበረሰብ እና በኩዊር ማህበረሰብ ውስጥ እንዴት መንቀሳቀስ እንዳለባት ትልቅ ትምህርት አስተምሯታል። 

ካነሳናቸው ሃሳቦች መሃል ጥቂቱን ቀንጨብ አድርገን አስቀምጠነዋል፤ ሕዳር 1፥ 2014  ላይ ሲለቀቅ እንደምትሰሙት ተስፋ እናደርጋለን።

“[ተመሳሳይ ፆታን ማፍቀር] ሰዎች ኖርማል የሚሉት ነገር እንዳልሆነ አውቃለሁ። ስለዚህ ኤለመንተሪ እያለሁ ይሄ ነገር ልክ አለመሆኑን ዲፌንድ የማደርግበት መንገድ ያስፈልግኛል። እና ለዚህ መፍትሔ ያስብኩት እንደወንድ ብሆንስ ብዬ ነበር። … ነገሩ እየቀለለኝ መጣ።”

“’ወንዳወንድ’ መሆን በጣም ጉዳቶችም አሉት። ለምሳሌ ማንም መንገደኛ ሊሆን ይችላል። ማንም መንገደኛ ያንን ሰው ትርፍ ቃል ለመናገር የመጋበዝ የመቅለል አይነት ነገር እንደውም ከመነጋገር ያለፈ violence ድረስ የመድረስ ነገር፣ በቀላሉ ለመገመት … በጣም አጋልጦ ይሰጥሻል።”

“እኛ [ኩዊር] ማህበረሰብም ውስጥም ያሉ ከበፊት ከወንዶች የተማርናቸው ነገሮች “ወንዳወንድ“ሴቶች ላይ የመፈለግ ነገር [አለ]። ለምሳሌ  በቀላል ነገር ብነግርሽ ነገሮችን የመስራት ነገር ሊሆን ይችላል ምናልባት ብዙ “ወንዳወንድ“ሴቶች ሊሰሩት ይችላሉ፤ እኔም ደስ ይለኛል መስራት ግን “ወንዳወንድ“ ስለሆንሽ ብቻ ነገሮችን መስራት አለብሽ፤ ይሄን ነገር ወንድ ልጅ የሚሰራውን ነገር በተለምዶ መስራት አለብሽ። ከሱ አልፎ በባህሪ እራስሽን አጋልጠሽ ላለማሳየት ኢሞሽናል ላለመሆን  ወንድ ልጅ አክት እንደሚያደርገው አድርጊ የምትባይበት ሁኔታ አለ። ይሄ ነገር ከውጪ ክማይረዳሽ ሰው ብቻ ሳይሆን ውስጥ የራሰሽ ከምትያቸው ከነገርሻቸው ኮሚኒቲ እና ፋሚሊ ካልሻቸው ሰዎችም የሚመጣብሽ ነገር ነው።”

Leave a Reply