ከኡጋንዳ መሪዎች “LGBTQ ሰዎች ተቃራኒ ፃታ አፍቃሪያንን ተመሳሳይ ፃታ አፍቃሪያን ማድረግ ይፈልጋሉ በሚለው የቆየ የተመሳሳይ ፃታ አፍቃሪያን ቅዥት ላይ በመመስረት ማንቂያዎችን ማንሳት” በጋና የቀረበው “እስከ ዛሬ እጅግ የከፋ የፀረ LGBTQ ህግ” ጨምሮ ላለፉት አመታት በአፍሪካ LGBTQ+ ሰዎች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ቀጥሏል።
ማህበራዊ አንቂዎች እና የተለያዩ LGBTQ+ ሰዎች በማንነታቸው እና በሚወዱት ምክንያት በመወንጀል ህይወታቸውን አጥተዋል:: ብዙዎች በወሲባዊ እና ስርዓተ ጾታ ማንነታቸው የተነሳ ነፃነታቸው ሲታፈን አይተዋል። በተለያዩ ተቋማት የሚደገፈው ጥላቻ በህይወታችን ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳደሩን ይቀጥላል ፣ እና እኛ ያለማቋረጥ በአፍሪካ ህዝባችን ላይ ለሚደርሱት ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንደ ዋነኛ ምክንያት ተደርገን እንዘለፋለን::
ይህ በአፍሪካ ውስጥ ያለነውን LGBTQ+ ማህበረሰብ አባላት ሊያስደነግጠን ይችላል ነገር ግን በፅናት እና ማንነታችንን በሚያስከብር መልኩ ህይወታችንን መምራት መቀጠል ይኖርብናል::
በአውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር መሰረት አዲሱን አመት ለምታከብሩ፣ ወደ አዲሱ አመት ስትገቡ ይህ የተስፋ መልእክታችን ነው። መገዛትን መቃወማችንን የምንቀጥል ጠንካራ ሰዎች መሆናችንን እናስታውስ። ህይወታችንን በእውነት እና በታላቅ ክብር መኖራችንን እንቀጥላለን።
መልካም በዓል
Like this:
Like Loading...
Related
Published by Queer Ethiopia
"Queer family" is an alternative space created by a group of queer Ethiopian women. It is designed to be a space for a diverse group of Ethiopian queer women whose sexual and gender identifications vary. It includes cis and trans women who may be lesbian, bisexual or asexual. This is a space where the experiences of queer people takes center stage. We hope to include personal experiences from our daily lives as queer people, various stories, interviews, original artwork and poetry. We hope it will also serve as a place where Ethiopians in Ethiopia and Ethiopians in the diaspora come as themselves to explore and create an online community.
If you would like to send us something, please send us an email via etqueerfamily@gmail.com
«ኩዊር ኢትዮጵያ» የተለያዩ ፆታዊና ወሲባዊ ዝንባሌ ላላቸው ኢትዮጵያዊ ኩዊር ሴቶች እንዲሆን ታስቦ በኩዊር ሴቶች የተመሠረተ አማራጭ ምኅዳር ነው። ይኽውም ሌዝቢያን፣ ባይሴክሽዋል ወይም ኤሴክሽዋል የሆኑ ሴቶችንንና ትራንስ ሴቶችን ያካትታል። ይህ ምኅዳር የኩዊር ማኅበረሰብ ታሪክ እና የሕይወት ልምድ ትልቅ ሥፍራ የሚይዝበት ነው። እንደ’ኩዊር ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወታችንን ገጠመኞች፤ የተለያዩ ሰዎችን የግል ታሪኮች፤ ቃለ-
መጠይቆች እንዲሁም ሥነ-ጥበባትን እንደምናካትት ተስፋ እናደርጋለን። ከነዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዳያስፖራ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ራሳቸውን ሆነው
የሚመጡበት የበይነ-መረብ ማኅበረሰብ መድረክ ሆኖ እንዲያገለግል ማስቻል ፍላጎታችን ብቻ ሣይሆን ጥረታችንም ጭምር ነው።
etqueerfamily@gmail.com
View all posts by Queer Ethiopia