ብቻዬን ስሆን ያለምንም ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ራሴን የሆንኩ ሰው ነኝ፤ ነገር ግን ከፍቅር አጋር ጋር ስሆን እደነግጣለሁ ምክንያቱም ለእነሱ እፈራላቸዋለሁ ከኔ ጋር ስለሆኑ ሰዎች እንዲተናኮሏቸው ወይም እንዲሰድቧቸው አልፈልግም። የሚረብሽ እና ግር የሚል ስሜት ነው።
አሁን ላይ የምከተላቸው ሶስት ህጎችን አውጥቻለሁ (በፍቅር ግንኙነት ዙሪያ)፥ የመጀመሪያው ራሳቸውን ካልቻሉ ሴቶች ጋር የፍቅር ግንኙነት አይኖረኝም፣ ሁለተኛው ከማንነታቸው ጋር ሙሉ ለሙሉ ካልታረቁ ሴቶች ጋር የፍቅር ግንኙነት አይኖረኝም ሶስተኛው ደግሞ መንፈሳዊ ሰላም የሌላቸው ሴቶች ጋር የፍቅር ግንኙነት አልጀምርም። ይሄንን ህግ ያወጣሁት ከበፊት ገጠመኖች በመነሳት ነው፤ ገሃነምን አይቼ የተመለስኩባቸው ገጠመኞች ናቸው። ስለዚህ አሁን ላይ እነዚህ ሶስት ነገሮችን ካላሟላች ሴት ጋር የፍቅር ግንኙነት አልመሰርትም:: ይገባኛል ከምንኖርበት ሃገር አንፃር እነዚህን መጠየቅ ብዙ ነው፥ የምናምነው፣ ባህሉ እና ያደግንበት ሁኔታ እንዲሁም የሃይማኖቱ ሆሆይታ ራሳችንን የምናይበት መንገድ ምናምን ነገር ግን እንደበፊቱ ሰላሜን መስዋዕት ላደርግ አልችልም፤ ከሁሉም በላይ ትልቅ ዋጋ የምሰጠው ነገር ነው።
Like this:
Like Loading...
Related
Published by Queer Ethiopia
"Queer family" is an alternative space created by a group of queer Ethiopian women. It is designed to be a space for a diverse group of Ethiopian queer women whose sexual and gender identifications vary. It includes cis and trans women who may be lesbian, bisexual or asexual. This is a space where the experiences of queer people takes center stage. We hope to include personal experiences from our daily lives as queer people, various stories, interviews, original artwork and poetry. We hope it will also serve as a place where Ethiopians in Ethiopia and Ethiopians in the diaspora come as themselves to explore and create an online community.
If you would like to send us something, please send us an email via etqueerfamily@gmail.com
«ኩዊር ኢትዮጵያ» የተለያዩ ፆታዊና ወሲባዊ ዝንባሌ ላላቸው ኢትዮጵያዊ ኩዊር ሴቶች እንዲሆን ታስቦ በኩዊር ሴቶች የተመሠረተ አማራጭ ምኅዳር ነው። ይኽውም ሌዝቢያን፣ ባይሴክሽዋል ወይም ኤሴክሽዋል የሆኑ ሴቶችንንና ትራንስ ሴቶችን ያካትታል። ይህ ምኅዳር የኩዊር ማኅበረሰብ ታሪክ እና የሕይወት ልምድ ትልቅ ሥፍራ የሚይዝበት ነው። እንደ’ኩዊር ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወታችንን ገጠመኞች፤ የተለያዩ ሰዎችን የግል ታሪኮች፤ ቃለ-
መጠይቆች እንዲሁም ሥነ-ጥበባትን እንደምናካትት ተስፋ እናደርጋለን። ከነዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዳያስፖራ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ራሳቸውን ሆነው
የሚመጡበት የበይነ-መረብ ማኅበረሰብ መድረክ ሆኖ እንዲያገለግል ማስቻል ፍላጎታችን ብቻ ሣይሆን ጥረታችንም ጭምር ነው።
etqueerfamily@gmail.com
View all posts by Queer Ethiopia