“ይሄንን ማህብረሰብ ሰፋ ለማድረግ ብንሰራ ጥሩ ነው ።ምክንያቱም እኔ ራሴ አዲስ አበባ ተወልጄ ያድኩት ግን ክፍለ ሃገር ነው ። እና ክፍለ ሃገር በነበርኩበት ሰዓት በጣም ብዙ የእኛ ማህበረሰብ አሉ፣ በጣም ሌዝቢያኖች አሉ ግን ጓደኛ ፈልገው ወይ ሰው ፈልገው እንኳን አያገኙም። ይሄንን ነገር ከእርግማን ጋር አያይዘውት እየሄዱ ነው። አዲስ አበባ ስትመጪና እና ሌላ ሴቶች ስታገኚ ግን ለካ ይሄ ነገር የእውነት ነው ነው የምትይው። ወንዶች ጥሩ እየሄደላቸው ነው ሴቶች ግን ወደኋላ እየቀረን ስለሆነ በየሙያችን ብንተባበበር የሆነ ነገር ማድረግ ይቻላል። በእርግጥ ስድብ ይመጣል ግን አሁንም እየተሰደብን ነው መሰደባችን ላይቀር ይስደቡን እኛ ደግሞ ስራውን በደንብ እንስራ።
ጌ ጓደኞች አሉኝ። የራሳቸው የሆነ ቦታ አላቸው እና እነሱ ቦታ ጋር እየሄድኩኝ ስዕሎቼን እሰራለሁ ማንም አይናገረኝም ፤ እንደውም ያደንቁኛል፤ አንቺ ልጅ እየጎበዝሽ ነው አይነት ነገር። ሴቶችም ይኖራሉ ብዬ አስባለሁ የተለያየ ታለንት ያላቸው እና ህብረት ኖሮን አብረን ብንሰራ በጣም ደስ ይለኛል። ምክንያቱም ፈቃደኛ ነኝ!”
Like this:
Like Loading...
Related
Published by Queer Ethiopia
"Queer family" is an alternative space created by a group of queer Ethiopian women. It is designed to be a space for a diverse group of Ethiopian queer women whose sexual and gender identifications vary. It includes cis and trans women who may be lesbian, bisexual or asexual. This is a space where the experiences of queer people takes center stage. We hope to include personal experiences from our daily lives as queer people, various stories, interviews, original artwork and poetry. We hope it will also serve as a place where Ethiopians in Ethiopia and Ethiopians in the diaspora come as themselves to explore and create an online community.
If you would like to send us something, please send us an email via etqueerfamily@gmail.com
«ኩዊር ኢትዮጵያ» የተለያዩ ፆታዊና ወሲባዊ ዝንባሌ ላላቸው ኢትዮጵያዊ ኩዊር ሴቶች እንዲሆን ታስቦ በኩዊር ሴቶች የተመሠረተ አማራጭ ምኅዳር ነው። ይኽውም ሌዝቢያን፣ ባይሴክሽዋል ወይም ኤሴክሽዋል የሆኑ ሴቶችንንና ትራንስ ሴቶችን ያካትታል። ይህ ምኅዳር የኩዊር ማኅበረሰብ ታሪክ እና የሕይወት ልምድ ትልቅ ሥፍራ የሚይዝበት ነው። እንደ’ኩዊር ማኅበረሰብ የዕለት ተዕለት ሕይወታችንን ገጠመኞች፤ የተለያዩ ሰዎችን የግል ታሪኮች፤ ቃለ-
መጠይቆች እንዲሁም ሥነ-ጥበባትን እንደምናካትት ተስፋ እናደርጋለን። ከነዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዳያስፖራ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ራሳቸውን ሆነው
የሚመጡበት የበይነ-መረብ ማኅበረሰብ መድረክ ሆኖ እንዲያገለግል ማስቻል ፍላጎታችን ብቻ ሣይሆን ጥረታችንም ጭምር ነው።
etqueerfamily@gmail.com
View all posts by Queer Ethiopia