(ክፍል ሁለት)
ይህ የሦስት ተከታታይ ክፍል ፁሑፍ ሁለተኛ ክፍል ነው።
ጠዋት ስራ ባይኖርም ጓደኛችን ጉዳይ አለኝ ደርሼ ልምጣ ብላ ወጣች እኛ ተነስተን ወደ አዲሱ ቤታቸው ሄደን፣ ከቤተሰቦቿ ጋ ቁርስ በልተን ጨዋታችንን አደራነው ቆይቼ “በቃ ልሂድ ብዙ ቆየሁ ” አልኩ “ለምን ? ትንሽ ቆይተን ፀሃይ ሲበርድ አብረን እንወጣለን” አለቺኝ ፣ እንደዛ ከሆነ ትንሽ ልተኛ አልኳት መኝታ ቤት አስገባችኝ ትንሽ ቆይታ መጣችና አልጋው ላይ ጋደም አለች፣ አቀፈችኝ ዝም ብዬ አየኋት “ሳሚኝ ” አልኳት። ፊቷ ፍም ሆነ ግራ ገባት ፣ ሳምኳት ዝም አለችኝ ቆይታ ግን መልሳ ሳመቺኝ ከዛ በኋላ ግን ማቆም አልፈለገችም።
በዚህ ሁሉ ግን እኔም ራሴን አላመንኩም ፣ አልተቀበልኩም እሷም እንደዛው። ቍስ ያለ እና ግራ ግብት ያለው ነገር ውስጥ ገባን። መለያየት አንችልም ፣ እኔን አይናገሩኝም እሷን ያሸማቅቋታል ትበሳጫለች፤ እበሳጫለሁ። ምን እናድርግ?
ብዙ ጊዜ አብረን ማሳለፍ ጀመርን በጣም ተቀራረብን ፣ የነብስ ዓይነት ሳንገናኝ አንውልም ጊዜው አይበቃንም በዚህ መሃል እኔ ወደ ቢሮ እንደተቀየርኩ የሚገልፅ ደብዳቤ መጣልኝ እና ከስራ እንደወጣን ከሌሎች ጓደኞቻችን ጋ ተሰብስበን ሻይ እየጠጣን እንደዋዛ ቢሮ መቀየሬን ስነግራቸው እሷ ሳይታወቃት “ምን !” ብላ ጮኸች ቀለል አርጌ “የአንድ ታክሲ መንገድ እኮ ነው ብዙ አይርቅም ” አልኩ፣ እሷ ግን እያለቀሰች ጥላን ሄደች ስላላስብኩት በጣም ደነገጥኩ ሁሉም እኔ ላይ አፈጠጡ ትከሻዬን ሰብቄ ዝም አልኩ ። ጥቂት ቆይቼ ቻው አልኩና ወደ ቤት ሄድኩ ማታ ደወልኩላት “ተረጋጋሽ ?” አልኳት “ደህና ነኝ ይቅርታ ስላላስብኩት ነው” አለች “ችግር የለም ብዙ አልራኩም እንደዚ እምናፍቅሽ አልመሰለኝም ነበር” አልኳት ሳቀች ” ከባልሽ ተጣልተሽ ነው? ብሎ አጎቴ ሙድ ያዘብኝ ” አለች “ምን አልሽው ” ስላት “ያው በለው አልኩታ ” አለቺኝ። ርዕሱን ዘልዬ ሌላ ሌላ ብዙ አወራን ፍቅረኛ አላት፣ ምን ማድረግ እንዳለብኝም ስላላወኩ እንዳልገባኝ ሆንኩ ብቻ በየቀኑ ረጅም ስልክ እናወራለን፣ በቻለችው ሁሉ ምሳ ሰዓት አብረን ነን ቀስ እያለች ገባችልኝ ፤ ወድጃታለሁ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግን አላውቅም።
ከጥቂት ጊዜ በኌላ ከፍቅረኛዋ ተለያየች እና ብዙ ጊዜ አብረን ነን ፣ ሌላ ሰው አትፈልግም ብቻዬን ነው ልታገኘኝ የምትፈልገው ውሎ እና አዳራችንን በዝርዝር እናወራለን ቤተሰብ ሆንን እሷም ወደ እኛ ቢሮ መጣች አንድ ቢሮ ሆንን ማለት ነው ፤ እኛ ቤት እነሱ ቤት በብዛት እናድራለን ሰበብ ነው የምንፈልገው። በዚህ መሃል እናቷ ለስራ ከሃገር ልትወጣ ስለሆነ የቤቱም ትልቅ እሷ ስለሆነች በአደራ አልፎ አልፎ እንዳያቸው ጠየቀችኝ ፤ እሺ አልኩ።
አብረን የምናሳልፈው ጊዜ ብዙ ሆነ አይሰለቸንም ፣ ውለን አድረን መለያየት አንችልም አስተያየቷ ያሳዝነኛል ፣ አፍቃሪ ናት ግን ደግሞ ግራ ተጋባን ለግንኙነታችን ስም አልሰጠነውም። አፈቅርሻለሁ ብያት አላውቅም ፣ እሷም አትልም። ዓይኖቻችን ግን መደበቅ አልቻሉም እኛ ሳንለው ቢሮ ሁሉም ሰው አወቀው አወራው ዋና ተቃዋሚያችን ደግሞ ጓደኛችን ናት። በዚህ ሁሉ ግን እኔም ራሴን አላመንኩም ፣ አልተቀበልኩም እሷም እንደዛው። ቅውስ ያለ እና ግራ ግብት ያለው ነገር ውስጥ ገባን። መለያየት አንችልም ፣ እኔን አይናገሩኝም እሷን ያሸማቅቋታል ትበሳጫለች፤ እበሳጫለሁ። ምን እናድርግ?
በዚህ ደግሞ ፈጣሪዬን አሳዘንኩት ብዬ እፀልያለሁ እደነግጣለሁ። ቤተሰቦቼ በዚህ መልኩ እንዲያዩን እና እንዲያዝኑ አልፈልግም ፤ እሷንም ማጣት ለኔ ከባድ ነው። ብቻ እማይጨበጥ ሆነብን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው እንደዚህ ያለ ነገር ውስጥ የገባሁት ፣ ብዙ ጊዜ አንድ ላይ መሆናችን ሌላ ሰው አለማስገባታችን ሃሜቱን አጦፈው ፣ ሁሉም ሰው ስለ እኛ ያወራል። እኛ ግን የለንም በራሳችን ዓለም ጠፍተናል ፤ በዚህ ሁሉ መሃል ሃሜቱ ጣራውን ሲያልፍ የሰው አስተያየት ሲቀየርብን፣ መግባባት እያቃታን ከራሳችን ተጣልተን እርስ በርስ መግባባት አቃተን እና አልፎ አልፎ አንዳንዴ ሃሜቱን ፍራቻ እሷ ከሌላ ወንድ ጋ መውጣት መሞከር ጀመረች። ቅናቴን እና ችላ መባሌን ለመቋቋም ሞከርኩ፣ የማህበረሰቡ ግፊት እሷም የምትቋቋመው አልነበረም። በሌላ በኩል ደሞ ሁለታችንም ራሳችንን መቀበል ፈርተናል ፣ ከባድ ነበር በቆራጥነት ኖ ማለትም አልቻልኩም:: ምን ብዬ እንደማሳምናት የማውቀው ነገር አልነበረም ፣ ዝም ስላት ታዝናለች፣ ለምን ስላት ሃሜቱስ ትለኛለች። እንዳንዴ እየሳመቺኝ ታለቅሳለች።
ይቀጥላል …