Skip to content Skip to footer

ናይጄሪያዊው ክሮስድሬሰር ኤርያ ማማን ማስታወስ

በቲክቶክ ብዙ ተከታዮችን ያፈራው የ33 አመቱ ናይጄሪያዊ ክሮስድሬሰር ኤርያ ማማ በትላንትናው እለት መገደሉን ተከታዮቹ እና የናይጄሪያ ዜና ዘግባል።

እንደናይጄሪያ ያሉ አፍሪካ ሃገራት LGBTQ+ የሆኑ ሰዎች በተለያየ ጊዜ ብዙ አይነት ጥቃት እና መገለል  ይደርስባቸዋል:: በእነዚህ ሃገራት የኤልጂቢቲኪው+ ማንነቶች እንደወንጀል ቢቆጠሩም እን ኤርያ ማማ ያሉ ሁሉ የሃገሪቱ ዜጎች ስለሆኑ ብቻ የህግ ከለላ እና ፍትህ ይገባቸዋል። ከጥቂት ጊዜያት በፊት ኤርያም ጥቃት ደርሶብኛል ብሎ በቲክቶክ ገፁ እስከእነቁስሉ ቀርቦ ያለውን ሁኔታ ቢዘግብም የህግ ከለላን እና ፍትህን ሳያገኝ ቀርቷል።

የኤሪያ ቲክቶክ አዝናን ብቻ ሳይሆኑ አስተማሪ ነበሩ።  ለናይጄሪያውያን እና ለመላው አፍሪካውያን ክሮስድሬሰርስ የመታወቅን መድረክ  በመክፈት ብዙ ድጋፍን አበርክቷል። 

ለኤርያ ቤተሰብ፣ ጏደኞች እና ደጋፊዎች ሁሉ መፅናናትን እንመኛለን:: ጀግንነቱ እና ለLGBTQ+ መብት ያበረከተው አስተዋፅዖ ሁሉ መቼም አይረሳም።

ትግሉ ይቀጥላል!

Leave a Reply

Discover more from queerethiopia

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading