ለብዙ ኩዊር ሰዎች ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር በፍርሃት የተሞላ ነው። ጃምዚ – በተለምዶ ወንዳወንድ የምትባል ኩዊር ሴት – ከነበራት ስጋት እና ፍርሃት ለማዳን በስደት ወደ ኬንያ ሸሸች። ኢትዮጵያ ውስጥ ስጋት የፈጠረሩባትን ነገሮች እና ከሃገር እንድትወጣ ያስገደዷትን ገጠመኞች ትናገራለች።
በኬንያ እንዴት አዲስ ነፃነት እንዳገኘች ትናገራለች፣ የሴት ጓደኛዋን ያለፍርሃት በግልፅ መውደድም ችላለች። ሆኖም ኢትዮጵያን እና ትታው ለሄደችው ህዝብ እና ባህል ጥልቅ ናፍቆት ይሰማታል።
ታሪኳን እና በስደተኛነት የመኖር ፈተናዎችን ያዳምጡ።