Skip to content Skip to footer

“የጆሃንስበርግ ኩራት እንደ ኩዊር ኢትዮጵያዊ ተስፋ ይሰጠኛል”

አንድ ጓደኛዬ ዛሬ ጠዋት ስለ ጆሃንስበርግ ፕራይድ አንድ ሊንክ ላከችልኝ። ሰዎችን የሚያከብሩትን ምስል እና ቪዲዮ ስመለከት በግርምታ ተውጬ ነበር። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለች አንድ ኩዊር ሴት፣ ፅናታቸውንና አንድነታቸውን አደነቅኩኝ። በአፍሪካ ውስጥ የመጀመሪያው የፕራይድ በዓል የተከበረበት ቦታ ነው፣ እናም እራሳችን መሆን ከባድ በሆነበት አለም ውስጥ እንደ ደማቅ ብርሃን በርቶዋል። ሰዎች ፍቅርን እና ትክክለኛነትን ሲያከብሩ ሳይ፣ በዚህ ጉዞ ውስጥ ብቻዬን እንዳልሆንኩ ያስታውሰኛል። የጆሃንስበርግ ኩራት ሳይ ጉዳትን ሳልፈራ ማንነቴን የምገልጽበት የወደፊት ተስፋ እንድሰንቅ አነሳሳኝ።

የጆሃንስበርግ ኩራት እንደ ትንሽ ሰልፍ እንዴት እንደተጀመረ እና ቀስበቀስ ወደ ትልቅ ነገር እንዳደገ አነበብኩ። እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ፣ ኤልጂቢቲኪው+ መሆን ብዙ ተግዳሮቶች በሚገጥሙበት፣ ይህን የመሰለ አንድነት ተስፋ እንዲኖረኝ አድርጎኛል። ለራሳችን አስተማማኝ ቦታዎችን መፍጠር እና መደጋገፍ እንደምንችል ያሳየኛል። ጥላቻ እና አድልዎን የሚቃወም ሰው ሁሉ ጥንካሬያችንን ይጨምራል እናም ለእውነተኛ ለውጥ እንድንገፋ ይረዳናል። ይህ ብዙ ኪሎ ሜትሮች ብንራራቅም እንኳን ድጋፍ ሰጪ ማህበረሰቦችን መገንባት እንደምንችል ተስፋ ይሰጠኛል፣ አንድ ላይ ሆነንም ወደ ኋላ የሚጎትቱንን አመለካከቶች መቃወም እንደምንችል ያሳየኛል።

ጆሃንስበርግ ኩራት ታሪኩን ሲያከብር፣ የተስፋ ስሜት ይሰማኛል። እንደሌላው ሰው በግልፅ መኖር እና በማንነቴ መኩራት እፈልጋለሁ። ይህ በዓል ማንነቴ ተቀባይነት ያገኘበትን የወደፊት ህልም እንድመኝ ያበረታታኛል።

የጆሃንስበርግ ኩራትን መመልከቴ ኢትዮጵያ ውስጥ የራሴን ቦታ እንድፈጥር አነሳስቶኛል። አንድ ላይ ሁሉም ሰው በኩራት “ይህ እኔ ነኝ” የሚልበት ቦታ መገንባት እንደምንችል ይሳየኛል።

Leave a Reply

Discover more from queerethiopia

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading