ደረሰ! የስነ-ተዋልዶ ዘመቻችንን ተከትሎ፣ አሁን በሁለቱም በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ የሚገኘውን የስነተዋልዶ ይዘን መጥተናል። መመሪያው በስነ ተዋልዶ ጤና እና መብቶች ዙሪያ ግንዛቤን ለማስጨበጥ፣ ለማስተማር እና ለመደገፍ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። መመሪያው የስነ ተዋልዶ ጤና፣ የመከላከያ እንክብካቤ እና ምርመራ፣ በግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚተላለፉ ኢንፌክሽኖች (STIs) እና ኤችአይቪ/ኤድስ እና የተለመዱ የስነ ተዋልዶ ጤና ሁኔታዎችን ያጠቃልላል።
ይህ መመሪያ ጠቃሚ፣ አበርቺ እና ትንሽ እንኳ የሚያረጋጋ እንዲሆን ምኞታችን ነው። የሚፈልጉትን ይውሰዱ፣ የሚችሉትን ያጋሩ፣ እና መማርዎን ይቀጥሉ።
ምክንያቱም እውቀት፣ ድጋፍ እና በራስ መኩራት ስለሚገባችሁ።