ዛሬ የአለም የስደተኞች ቀን እየተከበረ ነው፣ እኛም የኩዊር ኢትዮጵያውያን ስደተኛ ማህበረሰብ ለማክበር እና ጉዳዩ ላይ ግንዛቤን ለማሳደግ ልዩ እትም ይዘን መጥተናል።
ብዙ ኩዊር ኢትዮጵያውያን ደህንነት እና ነፃነትን ፍለጋ አገራቸውን ጥለው ይሰዳዳሉ። ሆኖም ወደ አዲስ ሕይወት የሚደረገው ጉዞ ብዙ ጊዜ ከራሱ ፈተናዎች እና መስዋዕቶች ጋር ይመጣል። ይህ እትም የኩዊር ኢትዮጵያውያንን ስደተኞች ህይወት የቀረጸውን ፍቅር እና አስቸጋሪ ምርጫዎች ያትታል፡፡
ላለፉት ሁለት ወራት፣ ኩዊር ኢትዮጵያ የዕለት ተዕለት ሕይወታቸውን በፎቶግራፍ መግለጽ እንዲችሉ ለተሳታፊዎች ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፤ ለአንባቢያን ፎቶግራፎቹ የተሳታፊዎችን ሕይወት ምን እንደሚመስል ማየት እንዲችሉ ይረዳል።
የተመረጡት ፎቶግራፎች እና ታሪኮች ይህንን ልዩ እትም የእውነትም ልዩ ያደርገዋል!
የአለም የስደተኞች ቀንን በማስመልከት የኩዊር ኢትዮጵያዊያን ስደተኛ ማህበረሰብ ድፍረት እና ጥንካሬ ለማክበር ስለተባበሩን እናመሰግናለን።
መልካም ንባብ!