ብዙ ኩዊር ሰዎች ከሚገጥሟቸው ፈተናዎች አንዱ እራሳቸውን የመግለፅ ሂደት ነው፣ በተለይ ለቤተሰብ አባላት። የሓበን ለአባቷ ኩዊርነቷን የመግለጥ ውሳኔ ለዚህ ፈታኝ ጉዞ ጠንካራ ምስክር ሆኖ ያገለግላል። በዚ በአዲሱ የኢትዮኩዊር ፖድካስት ሓበን ገጠመኞቿን ታካፍላለች እናም በርካታ ጠቃሚ ጥያቄዎችንም ትመልሳለች። ለአባቷ ራሷን መግለፅ ምን ይመስል ነበር? ይህን እርምጃ እንድትወስድ ያነሳሳት ምንድን ነው? እሳቸውስ ምን ምላሽ ሰጡ? ለሌሎች ኩዊር ኢትዮጵያውያንስ ምን ምክር ትሰጣለች?
ይህ ከልብ የመነጨ ውይይት ራሳችንን የመግለጥ ጉዞዎች ስንጓዝ ተስፋን እና ጥንካሬን ይሰጣል።
ይህ ውይይት እንደሚያስደስቶት ተስፋ እናደርጋለን።