ስለ አንድ በቅርብ ጊዜ ስላገቡ የማውቃቸው ሌዝቢያን ጥንዶች ብዙ አስቤ ነበር። መጀመሪያ ላይ ግንኙነታቸው በጣም በፍጥነት እየሄደ ስለ ነበር ሃሳብ ገብቶኝ ነበር – ከተገናኙበት ጊዜ አንስቶ ትዳር ውስጥ ለመድረስ በጣም የተቻኩሉ መሰለኝ። ግን ባሰብኩት ቁጥር ይህንን ውሳኔ ለመወሰን መነሻቸው ይገባኛል።
የኤልጂቢቲኪው+ ማህበረሰብ አባል ሲሆኑ፣ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የተቃራኒ ፆታ አፍቃሪያንን ጠል ማህበረሰብ ውስጥ ፍቅርን ማግኘት በጣም ከባድ ሊሆን ይችላል። ግንኙነቱን ሲያገኙ አጥብቀው ለመያዝ በመፈለጋቸው በፍጹም ልወቅሳቸው አልችልም።
በእንደዚህ አይነት ሁከት በበዛበት ቦታ ኩዊር የመሆን ፈተና ቢገጥማቸውም እንዴት አብረው ቤት እና ህይወት መገንባት እንደቻሉ ማየቴ በጣም ያስደስተኛል። እንደ LGBTQ+ ሰው መጠናናት እና መውደድ በጣም ከባድ ነው። ስለዚህ ይህን ውብ ግንኙነት ሲፈጥሩ ማየት ብዙ ተስፋ ይሰጠኛል። ለወደፊትም ለሁላችንም ተስፋ ይሰጠናል።